Archive for the ‘አማርኛ ዜና’ Category
የዩጋንዳ ፖሊስ ፍንዳታውን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ጥቃቶቹ በሁለት አጥፍቶ ጠፊዎች መከናወናቸውን አስታውቆ፤ በጥርጣሬ የተያዙት ኢትዮጵያዊያን መለቀቃቸውን አረጋግጧል።
የፖሊሱ አዛዥ ካሌ ካይ-ሁራ ለጋዜጠኞች ሲናገሩ በፍንዳታው ከተሰበሰቡት አስከሬኖች መካከል የሁለቱን ሬሳ ፈልጎ የመጣ ሰው አልተገኘም። የሁለቱን ሰዎች ማንነት የሚያሳዩ ምስሎችንም ፖሊስ አሳይቷል።
በአለም አቀፍ የወንጀለኛ አዳኝ ፓሊስ ኢንተር-ፖል ድረ ገጽ የሚገኙት እንደገና የተሰሩ ምስሎች የአጥፍቶ ጠፊዎቹን ማንነት ከሞላ ጎደል እንደሚያሳዩም ተጠቁሟል። አንደኛው ሰው ሶማሊያን ጨምሮ ከአፍሪካ ቀንድ ሰዎች የፊት ምስል ጋር የሚቀራረብ የቆዳ ቀለም ያለው ሰው ሲሆን፤ ሌላኛው ሰፋ ያለ ፊትና ጥቁር የቆዳ ቀለም ያለው ነው።
የፖሊሱ አዛዥ ካሌ ካይሁራ እነዚህ ሰዎች የአጥፍቶ ጠፊዎች መሆናቸውን በእርግጠኝነት ይናገራሉ።
“እነዚሁ ሁለት አስከሬኖች፤ ከሌሎቹ ሬሳዎች በተለየ መልኩ፤ መጥቶ ስጡን ያለ ሰው የለም። አሁን አንድ ሳምንት ሆኗል። ሁሉም አስከሬኖች በዘመድ ተለይተው ርክክብ ተደርጓል። እነዚህን የጠየቀ የለም፤ ይሄ ደግሞ አጋጣሚ ሊሆን አይችልም፣” ብለዋል። Read the rest of this entry »
Here is the Music Player. You need to installl flash player to show this cool thing!
Aend-Ethiopia Radio Address (Ethiopian 4th General Election 2010)
Aend Ethiopia Radio
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14 2002 (ሬዲዮ ፋና) የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ግንቦት 15 ቀን የተካሄደውን አራተኛ ዙር ጠቅላላ አገር አቀፍ ምርጫ የመጨረሻ ውጤት ዛሬ ይፋ አደረገ ።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካሉት 547 መቀመጫዎች መካከል የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር(ኢህአዴግ) 499 መቀመጫዎችን አግኝቷል ። ዛሬ ቦርዱ የምርጫውን የመጨረሻ ውጤት ይፋ ባደረገበት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እንዳሉት በመራጭነት ከተመዘገበው ከ31 ሚሊዮን ከሚበልጠው ህዝብ መካከል 29 ነጥብ 8 ሚሊዮኑ ማለትም 93.4 በመቶው ድምፁን ሰጥተቷል። Read the rest of this entry »
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14 2002 (ሬዲዮ ፋና) ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን በሰባት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ዶላር አዲስ አበባ ውስጥ ለሚያስገነባው ሕንጻ የመሰረት ድንጋይ አኖሩ፡፡ የኮሚሸኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ አብዱላሂ ጃኒን በስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት በካዛንቺስ አካባቢ የኢትዮጵያ መንግስት ለድርጅቱ በሰጠው ስፍራ ላይ የሚገነባው አዲስ ህንጻ ሁለት ዓመት በማይሞላ ጊዜ ውሰጥ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ Read the rest of this entry »

EthioGreen
![Uganda_bombers[1]1](http://www.aend-ethiopia.com/wp-content/uploads/2010/07/Uganda_bombers11.jpg)


